የጨረታ ማስታወቂያ

SC/L/WRM/003/2016

ኢትዮ ቴሌኮም አዳዲስ እና ከአገልግሎት የተመለሱ የተለያዩ የሞይባል እና መደበኛ ስልክ ቀፎዎች፣ የተለያዩ የመኪና መለዋወጫዎች፣ የተለያዩ ፖወር ዕቃዎች፣ የእንጨት ፖሎች፣ የሥራ መገልገያ መሳሪያዎች፣ የኘሪንተር ቀለሞች፣ የኔትወርክ ዕቃዎች፣ የቢሮ ፈርኒቸሮች፣ የኢንፎርሜሽን ሲስተም ዕቃዎች፣ ያገለገሉ ሴራሚክሶችን፣ ቁርጥራጭ ካርቶኖችን ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል። በመሆኑም ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከግንቦት 27 ቀን 2016 ዓ.ም እስከ ሰኔ 12 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ድረስ በማንኛውም ጊዜ እና ሰዓት ከ extratenders.com፣ 2merkato.com እና afrotendercom ዌብ ሳይቶች በቴሌ ብር አማካኝነት የማይመለስ 300.00 (ሶስት መቶ ብር ብቻ) በመክፈል እና በቀላሉ በመግዛት መወዳደር የምትችሉ ሲሆን በተጨማሪም ንብረቶቹን መመልከት እንዲሁም ተጨማሪ መረጃ ማግኘት የምትፈልጉ ተጫራቾች አዲስ አበባ በሚገኘው የኩባንያው ዕቃ ግምጃ ቤቶች (አቃቂ፣ አየር ጤና፣ ገርጂ እና ለገሀር) የታደሰ መታወቂያችሁን በመያዝ መጎብኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት አዲስ አበባ አቃቂ በሚገኘው የኩባንያው ዕቃ ግምጃ ቤት ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ላይ ይከፈታል። ኩባንያው የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

Share This Post:

Share on facebook
Share on telegram
Share on twitter
Share on linkedin

Follow Us

Recent Posts

Archives